1
አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡
2
ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው (ጌታህ ስም)፡፡
5
ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን፡፡
7
ራሱን የተብቃቃ (ባለ ሀብት) ኾኖ ለማየቱ፡፡
11
አየህን? ንገረኝ (ተከልካዩ) በትክክለኛ መንገድ ላይ ቢኾን፤
12
ወይም (ፈጣሪውን) በመፍራት ቢያዝ፤
13
አየህን? ንገረኝ (ከልካዩ) ቢያስተባብልና (ከእምነት) ቢሸሽ፤
15
ይተው ባይከለከል አናቱን ይዘን እንጎትተዋለን፡፡
16
ውሸታም ስሕተተኛ የኾነችውን አናቱን፡፡
18
(እኛም) ዘበኞቻችንን እንጠራለን፡፡
19
ይከልከል አትታዘዘው፡፡ ስገድም፤ (ወደ አላህ) ተቃረብም፡፡