3
በወላጂም በወለዳቸውም ሰዎች (በአዳምና በዘሮቹ ሁሉ እምላለሁ)፡፡
4
ሰውን ሁሉ በእርግጥ በልፋት ውስጥ ኾኖ ፈጠርነው፡፡
5
በእርሱ ላይ አንድም የማይችል መኾኑን ይጠረጥራልን?
8
ለእርሱ ሁለት ዓይኖችን አላደረግንለትምን?
12
ዓቀበቲቱም (መውጣቷ) ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
14
ወይም የረኃብ ባለቤት በኾነ ቀን ማብላት፡፡
16
ወይም የዐፈር ባለቤት የኾነን ድኻ (ማብላት ነው)፡፡
17
(ዐቀበቲቱን አልወጣም)፡፡ ከዚያም ከነዚያ ከአመኑትና በመታገስ አደራ ከተባባሉት፣ በማዘንም አደራ ከተባባሉት ሰዎች አልኾነም፡፡
18
እነዚያ (ይህንን የፈጸሙ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡
19
እነዚያም በአንቀጾቻችን የካዱት እነርሱ የግራ ጓዶች ናቸው፡፡
20
በእነርሱ ላይ የተዘጋች እሳት አልለች፡፡