Ana SayfaMealler › M.Sadiq and M.Sani Habib
MS

M.Sadiq and M.Sani Habib

M.Sadiq and M.Sani Habib
M.Sadiq and M.Sani Habib meali ile okumaya başla
Fecr 1 / 30
1
በጎህ እምላለሁ፡፡
M.Sadiq 89:1
2
በዐሥር ሌሊቶችም፡፡
M.Sadiq 89:2
3
በጥንዱም በነጠላውም፡፡
M.Sadiq 89:3
4
በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡
M.Sadiq 89:4
5
በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን?
M.Sadiq 89:5
6
ጌታህ በዓድ እንዴት እንደ ሠራ አታውቅምን?
M.Sadiq 89:6
7
በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡
M.Sadiq 89:7
8
በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡
M.Sadiq 89:8
9
በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡
M.Sadiq 89:9
10
በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡
M.Sadiq 89:10
11
በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡
M.Sadiq 89:11
12
በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?)
M.Sadiq 89:12
13
በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡
M.Sadiq 89:13
14
ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡
M.Sadiq 89:14
15
ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡
M.Sadiq 89:15
16
በሞከረውና በእርሱ ላይ ሲሳዩን ባጠበበ ጊዜማ «ጌታዬ አሳነሰኝ» ይላል፡፡
M.Sadiq 89:16
17
ይከልከል፤ ይልቁንም የቲምን አታከብሩም፡፡
M.Sadiq 89:17
18
ድኻንም በማብላት ላይ አትታዘዙም፡፡
M.Sadiq 89:18
19
የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡
M.Sadiq 89:19
20
ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡
M.Sadiq 89:20
21
ተዉ፤ ምድር ደጋግማ በተሰባበረች ጊዜ፤
M.Sadiq 89:21
22
መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ትዕዛዙ) በመጣ ጊዜ፤
M.Sadiq 89:22
23
ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?
M.Sadiq 89:23
24
«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡
M.Sadiq 89:24
25
በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡
M.Sadiq 89:25
26
የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡
M.Sadiq 89:26
27
(ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ!
M.Sadiq 89:27
28
«ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡
M.Sadiq 89:28
29
«በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡
M.Sadiq 89:29
30
ገነቴንም ግቢ፤» (ትባላለች)፡፡
M.Sadiq 89:30
Fecr suresi tamamlandı