2
ለእነዚያ ከሰዎች ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፡፡
3
ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡
4
እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?
6
ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡
7
በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡
8
ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
10
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
11
ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡
12
በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡
13
አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡
14
ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡
15
ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡
16
ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡
17
ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡
18
በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡
19
ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
22
እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡
23
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡
24
በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡
26
ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡
28
ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡
29
እነዚያ ያምመጹት በእነዚያ ባመኑት በእርግጥ ይስቁ ነበሩ፡፡
30
በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡
Sonraki 6 ayet →