Ana SayfaMealler › M.Sadiq and M.Sani Habib
MS

M.Sadiq and M.Sani Habib

M.Sadiq and M.Sani Habib
M.Sadiq and M.Sani Habib meali ile okumaya başla
Mutaffifın 1 / 36
1
ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡
M.Sadiq 83:1
2
ለእነዚያ ከሰዎች ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፡፡
M.Sadiq 83:2
3
ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡
M.Sadiq 83:3
4
እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?
M.Sadiq 83:4
5
በታላቁ ቀን፡፡
M.Sadiq 83:5
6
ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡
M.Sadiq 83:6
7
በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡
M.Sadiq 83:7
8
ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
M.Sadiq 83:8
9
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
M.Sadiq 83:9
10
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
M.Sadiq 83:10
11
ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡
M.Sadiq 83:11
12
በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡
M.Sadiq 83:12
13
አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡
M.Sadiq 83:13
14
ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡
M.Sadiq 83:14
15
ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡
M.Sadiq 83:15
16
ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡
M.Sadiq 83:16
17
ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡
M.Sadiq 83:17
18
በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡
M.Sadiq 83:18
19
ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
M.Sadiq 83:19
20
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
M.Sadiq 83:20
21
ባለሟልዎቹ ይጣዱታል፡፡
M.Sadiq 83:21
22
እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡
M.Sadiq 83:22
23
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡
M.Sadiq 83:23
24
በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡
M.Sadiq 83:24
25
ተጣርቶ ከታተመ ጠጅ ይጠጣሉ፡፡
M.Sadiq 83:25
26
ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡
M.Sadiq 83:26
27
መበረዣውም ከተስኒም ነው፡፡
M.Sadiq 83:27
28
ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡
M.Sadiq 83:28
29
እነዚያ ያምመጹት በእነዚያ ባመኑት በእርግጥ ይስቁ ነበሩ፡፡
M.Sadiq 83:29
30
በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡
M.Sadiq 83:30