Ana SayfaMealler › M.Sadiq and M.Sani Habib
MS

M.Sadiq and M.Sani Habib

M.Sadiq and M.Sani Habib
M.Sadiq and M.Sani Habib meali ile okumaya başla
Tekvir 1 / 29
1
ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤
M.Sadiq 81:1
2
ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤
M.Sadiq 81:2
3
ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤
M.Sadiq 81:3
4
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤
M.Sadiq 81:4
5
እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤
M.Sadiq 81:5
6
ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤
M.Sadiq 81:6
7
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤
M.Sadiq 81:7
8
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤
M.Sadiq 81:8
9
በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤
M.Sadiq 81:9
10
ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤
M.Sadiq 81:10
11
ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤
M.Sadiq 81:11
12
ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤
M.Sadiq 81:12
13
ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤
M.Sadiq 81:13
14
ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤
M.Sadiq 81:14
15
ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡
M.Sadiq 81:15
16
ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡
M.Sadiq 81:16
17
በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤
M.Sadiq 81:17
18
በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡
M.Sadiq 81:18
19
እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡
M.Sadiq 81:19
20
የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡
M.Sadiq 81:20
21
በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡
M.Sadiq 81:21
22
ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡
M.Sadiq 81:22
23
በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡
M.Sadiq 81:23
24
እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡
M.Sadiq 81:24
25
እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡
M.Sadiq 81:25
26
ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?
M.Sadiq 81:26
27
እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
M.Sadiq 81:27
28
ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡
M.Sadiq 81:28
29
የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡
M.Sadiq 81:29
Tekvir suresi tamamlandı