4
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤
7
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤
8
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤
14
ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤
15
ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡
16
ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡
17
በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤
18
በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡
19
እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡
20
የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡
21
በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡
22
ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡
23
በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡
24
እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡
25
እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡
27
እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
28
ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡
29
የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡