Ana SayfaMealler › M.Sadiq and M.Sani Habib
MS

M.Sadiq and M.Sani Habib

M.Sadiq and M.Sani Habib
M.Sadiq and M.Sani Habib meali ile okumaya başla
Abese 1 / 42
1
ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡
M.Sadiq 80:1
2
ዕውሩ ስለ መጣው፡፡
M.Sadiq 80:2
3
ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡
M.Sadiq 80:3
4
ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡
M.Sadiq 80:4
5
የተብቃቃው ሰውማ፤
M.Sadiq 80:5
6
አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡
M.Sadiq 80:6
7
ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡
M.Sadiq 80:7
8
እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤
M.Sadiq 80:8
9
እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤
M.Sadiq 80:9
10
አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡
M.Sadiq 80:10
11
ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡
M.Sadiq 80:11
12
የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡
M.Sadiq 80:12
13
በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡
M.Sadiq 80:13
14
ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡
M.Sadiq 80:14
15
በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡
M.Sadiq 80:15
16
የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡
M.Sadiq 80:16
17
ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?
M.Sadiq 80:17
18
(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)
M.Sadiq 80:18
19
ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡
M.Sadiq 80:19
20
ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡
M.Sadiq 80:20
21
ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡
M.Sadiq 80:21
22
ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡
M.Sadiq 80:22
23
በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡
M.Sadiq 80:23
24
ሰውም ወደ ምግቡ ይመልከት፡፡
M.Sadiq 80:24
25
እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡
M.Sadiq 80:25
26
ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤
M.Sadiq 80:26
27
በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤
M.Sadiq 80:27
28
ወይንንም፤ እርጥብ ያበቀልን፤
M.Sadiq 80:28
29
የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤
M.Sadiq 80:29
30
ጭፍቆች አትክልቶችንም፤
M.Sadiq 80:30