Ana SayfaMealler › M.Sadiq and M.Sani Habib
MS

M.Sadiq and M.Sani Habib

M.Sadiq and M.Sani Habib
M.Sadiq and M.Sani Habib meali ile okumaya başla
Naziat 1 / 46
1
በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤
M.Sadiq 79:1
2
በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤
M.Sadiq 79:2
3
መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤
M.Sadiq 79:3
4
መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤
M.Sadiq 79:4
5
ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
M.Sadiq 79:5
6
ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤
M.Sadiq 79:6
7
ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
M.Sadiq 79:7
8
በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡
M.Sadiq 79:8
9
ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡
M.Sadiq 79:9
10
«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡
M.Sadiq 79:10
11
«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»
M.Sadiq 79:11
12
«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡
M.Sadiq 79:12
13
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡
M.Sadiq 79:13
14
ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡
M.Sadiq 79:14
15
የሙሳ ወሬ መጣልህን?
M.Sadiq 79:15
16
ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤
M.Sadiq 79:16
17
ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡
M.Sadiq 79:17
18
በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»
M.Sadiq 79:18
19
«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡
M.Sadiq 79:19
20
ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡
M.Sadiq 79:20
21
አስተባበለም፤ አመጸም፡፡
M.Sadiq 79:21
22
ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡
M.Sadiq 79:22
23
(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡
M.Sadiq 79:23
24
አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»
M.Sadiq 79:24
25
አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡
M.Sadiq 79:25
26
በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡
M.Sadiq 79:26
27
ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡
M.Sadiq 79:27
28
ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡
M.Sadiq 79:28
29
ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡
M.Sadiq 79:29
30
ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡
M.Sadiq 79:30