5
ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
6
ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤
7
ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
8
በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡
9
ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡
10
«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡
11
«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»
12
«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡
14
ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡
16
ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤
17
ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡
18
በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»
19
«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡
22
ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡
23
(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡
24
አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»
25
አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡
26
በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡
27
ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡
29
ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡
Sonraki 16 ayet →