Ana SayfaMealler › M.Sadiq and M.Sani Habib
MS

M.Sadiq and M.Sani Habib

M.Sadiq and M.Sani Habib
M.Sadiq and M.Sani Habib meali ile okumaya başla
Mürselat 1 / 50
1
ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣
M.Sadiq 77:1
2
በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣
M.Sadiq 77:2
3
መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣
M.Sadiq 77:3
4
መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣
M.Sadiq 77:4
5
መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣
M.Sadiq 77:5
6
ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡
M.Sadiq 77:6
7
ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡
M.Sadiq 77:7
8
ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡
M.Sadiq 77:8
9
ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡
M.Sadiq 77:9
10
ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡
M.Sadiq 77:10
11
መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡
M.Sadiq 77:11
12
ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤
M.Sadiq 77:12
13
ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡
M.Sadiq 77:13
14
የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
M.Sadiq 77:14
15
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
M.Sadiq 77:15
16
የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?
M.Sadiq 77:16
17
ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡
M.Sadiq 77:17
18
በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
M.Sadiq 77:18
19
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
M.Sadiq 77:19
20
ከደካማ ውሃ አልፈጠርናችሁምን?
M.Sadiq 77:20
21
በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡
M.Sadiq 77:21
22
እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡ መጠንነውም፤ ምን ያማርንም
M.Sadiq 77:22
23
መጣኞች ነን!
M.Sadiq 77:23
24
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
M.Sadiq 77:24
25
ምድርን ሰብሳቢ አላደረግናትምን?
M.Sadiq 77:25
26
ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡
M.Sadiq 77:26
27
በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡
M.Sadiq 77:27
28
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
M.Sadiq 77:28
29
«ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡
M.Sadiq 77:29
30
«ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡
M.Sadiq 77:30