1
(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡
2
(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
3
ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?
4
አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡
5
ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡
6
«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡
10
«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡
12
በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
13
ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡
14
በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡
15
ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡
16
በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡
17
(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡
18
ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡
19
ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡
20
(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡
21
መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡
22
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡
24
ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡
25
በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡
26
ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤
27
«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡
28
(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡
30
በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ (ፍርድ) ነው፡፡
Sonraki 10 ayet →