6
ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ፤ (በረከትን) አትለግስለለ
8
በቀንዱም በተነፋ ጊዜ (ነገሩ ይበረታል)፡፡
9
ይህም (ጊዜ) ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡
10
በከሓዲዎች ላይ ገር ያልኾነ ነው፡፡
11
አንድ ኾኖ ከፈጠርኩት ሰው ጋር ተዎኝ (እኔ እበቃሃለሁ)፡፡
12
ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በያይነቱ) ያደረግሁለት፡፡
13
(በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡
14
ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡
16
ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡
18
እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡
20
ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ!
21
ከዚያም እንደ ገና (በቁርኣኑ ነገር) ተመለከተ፡፡
22
ከዚያም ፊቱን አጨፈገገ፤ አኮማተረም፡፡
24
አለም «ይህ (ከሌላ) የሚቀዳ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
25
«ይህ የሰው ቃል እንጅ ሌላ አይደለም፡፡»
26
በሰቀር ውስጥ በእርግጥ አገባዋለሁ፡፡
27
ሰቀር ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
28
(ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም አትተውምም፡፡
30
በእርሷም ላይ አሥራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት፡፡
Sonraki 26 ayet →