Ana SayfaMealler › M.Sadiq and M.Sani Habib
MS

M.Sadiq and M.Sani Habib

M.Sadiq and M.Sani Habib
M.Sadiq and M.Sani Habib meali ile okumaya başla
Mearic 1 / 44
1
ወዳቂ ከኾነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ፡፡
M.Sadiq 70:1
2
በከሓዲዎች ላይ (ወዳቂ ከኾነው) ለእርሱ መላሽ የለውም፡፡
M.Sadiq 70:2
3
የ(ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ (መላሽ የለውም)፡፡
M.Sadiq 70:3
4
መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺሕ ዓመት በኾነ ቀን ውስጥ ወደእርሱ ያርጋሉ፤ (ይወጣሉ)፡፡
M.Sadiq 70:4
5
መልካምንም ትዕግስት ታገሥ፡፡
M.Sadiq 70:5
6
እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል፡፡
M.Sadiq 70:6
7
እኛም ቅርብ ኾኖ እናየዋለን፡፡
M.Sadiq 70:7
8
ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን፡፡
M.Sadiq 70:8
9
ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን፡፡
M.Sadiq 70:9
10
ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)፡፡
M.Sadiq 70:10
11
(ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡
M.Sadiq 70:11
12
በሚስቱም በወንድሙም፡፡
M.Sadiq 70:12
13
በዚያችም በምታስጠጋው ጎሳው፡፡
M.Sadiq 70:13
14
በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡
M.Sadiq 70:14
15
ይተው! እርሷ (እሳቲቱ) ለዟ ናት፡፡
M.Sadiq 70:15
16
የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡
M.Sadiq 70:16
17
(ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች፡፡
M.Sadiq 70:17
18
ገንዘብን የሰበሰበንና (ዘካውን ሳይሰጥ) የቆጠረንም፤ (ትጠራለች)፡፡
M.Sadiq 70:18
19
ሰው ቅጠ ቢስ ኾኖ ተፈጠረ፡፡
M.Sadiq 70:19
20
ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጪተኛ፡፡
M.Sadiq 70:20
21
መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘ ጊዜ ከልካይ (ኾኖ ተፈጠረ)፡፡
M.Sadiq 70:21
22
ሰጋጆቹ ብቻ ሲቀሩ፡፡
M.Sadiq 70:22
23
እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘውታሪዎች የኾኑት፡፡
M.Sadiq 70:23
24
እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት፡፡
M.Sadiq 70:24
25
ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡
M.Sadiq 70:25
26
እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት (የሚያረጋግጡት)፡፡
M.Sadiq 70:26
27
እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የኾኑት፡፡
M.Sadiq 70:27
28
የጌታቸው ቅጣት (መምጣቱ) የማያስተማምን ነውና፡፡
M.Sadiq 70:28
29
እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡
M.Sadiq 70:29
30
በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በእነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡
M.Sadiq 70:30