Ana SayfaMealler › M.Sadiq and M.Sani Habib
MS

M.Sadiq and M.Sani Habib

M.Sadiq and M.Sani Habib
M.Sadiq and M.Sani Habib meali ile okumaya başla
Kalem 1 / 52
1
ነ.(ኑን)፤ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡
M.Sadiq 68:1
2
አንተ በጌታህ ጸጋ የተጎናጸፍክ ስትኾን ዕብድ አይደለህም፡፡
M.Sadiq 68:2
3
ላንተም (ከጌታህ) የማይቋረጥ ዋጋ በእርግጥ አልለህ፡፡
M.Sadiq 68:3
4
አንተም በታላቅ ጠባይ ላይ ነህ፡፡
M.Sadiq 68:4
5
ወደፊትም ታያለህ፤ ያያሉም፡፡
M.Sadiq 68:5
6
ዕብደት በማንኛችሁ እንዳልለ፡፡
M.Sadiq 68:6
7
ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም ተመሪዎቹን ዐዋቂ ነው፡፡
M.Sadiq 68:7
8
ለአስተባባዮችም አትታዝዙ፡፡
M.Sadiq 68:8
9
ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡
M.Sadiq 68:9
10
ወራዳንም ሁሉ አትታዘዝ፡፡
M.Sadiq 68:10
11
ሰውን አነዋሪንና በማሳበቅ ኼያጅን፡፡
M.Sadiq 68:11
12
ለበጎ ነገር በጣም ከልካይን፣ ወሰን አላፊን፣ ኃጢአተኛን፤
M.Sadiq 68:12
13
ልበ ደረቅን፣ ከዚህ በኋላ ዲቃላን (ሁሉ አትታዘዝ)፡፡
M.Sadiq 68:13
14
የገንዘብና የልጆች ባለቤት በመኾኑ (ያስተባብላል)፡፡
M.Sadiq 68:14
15
በእርሱ ላይ አንቀጾቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡
M.Sadiq 68:15
16
በአፍንጫው ላይ በእርግጥ (የሚነወርበት) ምልክት እናደርግበታለን፡፡
M.Sadiq 68:16
17
እኛ የአትክልቲቱን ባለቤቶቸ እንደ ሞከርን (የመካን ሰዎች) ሞከርናቸው፡፡ ማልደው (ፍሬዋን) ሊለቅሟት በማሉ ጊዜ፡፡
M.Sadiq 68:17
18
(በመሓላቸው) አያስቀሩምም፡፡
M.Sadiq 68:18
19
እነርሱ የተኙ ኾነውም ሳሉ ከጌታህ የኾነ ዟሪ በእርሷ ላይ ዞረባት፡፡
M.Sadiq 68:19
20
እንደ ሌሊት ጨለማም ኾና አነጋች፤ (ከሰለች)፡፡
M.Sadiq 68:20
21
ያነጉም ኾነው ተጠራሩ፡፡
M.Sadiq 68:21
22
«ቆራጮች እንደ ኾናችሁ በእርሻቸሁ ላይ ማልዱ» በማለት፡፡
M.Sadiq 68:22
23
እነርሱ የሚንሾካሾኩ ኾነው ኼዱም፡፡
M.Sadiq 68:23
24
ዛሬ በእናንተ ላይ ድኻ እንዳይገባት በማለት፡፡
M.Sadiq 68:24
25
(ድኾችን) በመከልከልም ላይ (በሐሳባቸው) ቻዮች ኾነው ማለዱ፡፡
M.Sadiq 68:25
26
(ተቃጥላ) ባዩዋትም ጊዜ «እኛ በእርግጥ ተሳሳቾች ነን» አሉ፡፡
M.Sadiq 68:26
27
«ይልቁንም እኛ የተከለከልን ነን» አሉ፡፡
M.Sadiq 68:27
28
ትክክለኛቸው «ለእናንተ አላህን ለምን አታጠሩም አላልኳችሁምን?» አላቸው፡፡
M.Sadiq 68:28
29
«ጌታችን ጥራት ይገባው፡፡ እኛ በዳዮች ነበርን፤» አሉ፡፡
M.Sadiq 68:29
30
የሚወቃቀሱም ኾነው ከፊሎቻቸው በከፊሉ ላይ መጡ፡፡
M.Sadiq 68:30