5
ፀሐይና ጨረቃ በተወሰነ ልክ (ይኼዳሉ)፡፡
6
ሐረግና ዛፍም (ለእርሱ) ይሰግዳሉ፡፡
7
ሰማይንም አጓናት፡፡ ትክክለኛነትንም ደነገገ፡፡
9
መመዘንንም በትክክል መዝኑ፡፡ ተመዛኙንም አታጉድሉ፡፡
11
በውስጧ እሸት ባለ ሺፋኖች የኾኑ ዘንባባዎችም ያሉባት ስትኾን፡፡
12
የገለባ ባለቤት የኾነ ቅንጣትም፡፡ ባለ መልካም መዐዛ ቅጠሎችም (ያሉባት ስትኾን)፡፡
13
(ሰዎችና ጋኔኖች ሆይ!) ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
14
ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ ጭቃ ፈጠረው፡፡
15
ጃንንም ከእሳት ከኾነ ነበልባል ፈጠረው፡፡
16
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
17
የሁለቱ ምሥራቆች ጌታ፤ የሁለቱ ምዕራቦችም ጌታ ነው፡፡
18
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
19
ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡
20
(እንዳይዋሐዱ) በመካከላቸው ጋራጅ አልለ፡፡ (አንዱ ባንዱ ላይ) ወሰን አያልፉም፡፡
21
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
23
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
24
እንደ ጋራዎች ኾነው በባሕር ውስጥ የተሠሩት ተንሻለዮቹም (ታንኳዎች) የእርሱ ናቸው፡፡
25
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
26
በእርሷ (በምድር) ላይ ያለው ሁሉ ጠፊ ነው፡፡
27
የልቅናና የልግሥና ባለቤት የኾነው የጌታህ ፊትም ይቀራል፡፡ (አይጠፋም)፡፡
28
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
29
በሰማያትና በምድር ውስጥ ያሉት ሁሉ ይለምኑታል፡፡ በየቀኑ ሁሉ እርሱ በሥራ ላይ ነው፡፡
30
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
Sonraki 30 ayet →