Ana SayfaMealler › M.Sadiq and M.Sani Habib
MS

M.Sadiq and M.Sani Habib

M.Sadiq and M.Sani Habib
M.Sadiq and M.Sani Habib meali ile okumaya başla
Tur 1 / 49
1
በጡር (ጋራ) እምላለሁ፡፡
M.Sadiq 52:1
2
በተጻፈው መጽሐፍም፡፡
M.Sadiq 52:2
3
በተዘረጋ ብራና ላይ፤ (በተጻፈው)፡፡
M.Sadiq 52:3
4
በደመቀው ቤትም፡፡
M.Sadiq 52:4
5
ከፍ በተደረገው ጣራም፡፡
M.Sadiq 52:5
6
በተመላው ባሕርም እምላለሁ፡፡
M.Sadiq 52:6
7
የጌታህ ቅጣት በእርግጥ ወዳቂ ነው፤ (የማይቀር ነው)፡፡
M.Sadiq 52:7
8
ለእርሱ ምንም ገፍታሪ የለውም፡፡
M.Sadiq 52:8
9
ሰማይ ብርቱ መዞርን በምትዞርበት ቀን (ይኾናል)፡፡
M.Sadiq 52:9
10
ተራራዎችም መኼድን በሚኼዱበት (ቀን)፡፡
M.Sadiq 52:10
11
ለአስተባባዮችም ያን ጊዜ ወዮላቸው፡፡
M.Sadiq 52:11
12
ለእነዚያ እነርሱ በውሸት ውስጥ የሚጫወቱ ለኾኑት፡፡
M.Sadiq 52:12
13
ወደ ገሀነም እሳት በኀይል መግገፍተርን በሚግገፈተሩበት ቀን፡፡
M.Sadiq 52:13
14
ይህቺ ያቺ በእርሷ ታስተባብሉባት የነበራችሁት እሳት ናት፡፡
M.Sadiq 52:14
15
ይህ (ፊት ትሉ እንደነበራችሁት) ድግምት ነውን? ወይስ እናንተ አታዩምን?
M.Sadiq 52:15
16
ግቧት ታገሱም ወይም አትታገሡ በእናንተ ላይ እኩል ነው፡፡ የምትምመነዱት ትሠሩት የነበራችሁትን (ፍዳ) ብቻ ነው (ይባላሉ)፡፡
M.Sadiq 52:16
17
አላህን ፈሪዎቹ በእርግጥ በገነቶችና በጸጋ ውስጥ ናቸው፡፡
M.Sadiq 52:17
18
ጌታቸው በሰጣቸው ጸጋ ተደሳቾች ኾነው (በገነት ውስጥ ናቸው)፡፡ የገሀነምንም ስቃይ ጌታቸው ጠበቃቸው፡፡
M.Sadiq 52:18
19
«ትሠሩት በነበራችሁት ምክንያት ተደሳቾች ኾናችሁ ብሉ፤ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡
M.Sadiq 52:19
20
በተደረደሩ አልጋዎች ላይ ተደጋፊዎች ኾነው (በገነት ይኖራሉ)፡፡ ዓይናማዎች በኾኑ ነጫጭ ሴቶችም እናጠናዳቸዋለን፡፡
M.Sadiq 52:20
21
እነዚያም ያመኑትና ዝርያቸውም በእምነት የተከተለቻቸው ዝርያቸውን በእነርሱ እናስጠጋለን፡፡ ከሥራቸውም ምንም አናጎድልባቸውም፡፡ ሰው ሁሉ በሠራው ሥራ ተያዢ ነው፡፡
M.Sadiq 52:21
22
ከሚሹትም ሁሉ እሸትንና ስጋን እንጨምርላቸዋለን፡፡
M.Sadiq 52:22
23
በውስጧ መጠጥን ይሰጣጣሉ፡፡ በውስጧ ውድቅ ንግግርና መውወንጀልም የለም፡፡
M.Sadiq 52:23
24
ለነርሱም የኾኑ ወጣቶች ልክ የተሸፈነ ሉል መስለው በእነርሱ ላይ (ለማሳለፍ) ይዘዋወራሉ፡፡
M.Sadiq 52:24
25
የሚጠያየቁ ኾነውም ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይዞራል፡፡
M.Sadiq 52:25
26
«እኛ ፊት በቤተሰቦቻችን ውስጥ (ከቅጣት) ፈሪዎች ነበርን» ይላሉ፡፡
M.Sadiq 52:26
27
«አላህም በእኛ ላይ ለገሰ፡፡ የመርዛም እሳት ቅጣትንም ጠበቀን፡፡
M.Sadiq 52:27
28
«እኛ ከዚህ በፊት እንለምነው ነበርን፡፡ እነሆ እርሱ በጎ ዋይ አዛኝ ነውና» (ይላሉ)፡፡
M.Sadiq 52:28
29
(ሰዎችን) አስታውስም፡፡ አንተም በጌታህ ጸጋ ምክንያት ጠንቋይም ዕብድም አይደለህም፡፡
M.Sadiq 52:29
30
ይልቁንም የሞትን አደጋ በእርሱ የምንጠባበቅበት የኾነ ባለ ቅኔ ነው ይላሉን?
M.Sadiq 52:30