Ana SayfaMealler › M.Sadiq and M.Sani Habib
MS

M.Sadiq and M.Sani Habib

M.Sadiq and M.Sani Habib
M.Sadiq and M.Sani Habib meali ile okumaya başla
Ta Ha 1 / 135
1
ጠ.ሀ. (ጣ ሃ)
M.Sadiq 20:1
2
ቁርኣንን ባንተ ላይ እንድትቸገር አላወረድንም፡፡
M.Sadiq 20:2
3
ግን አላህን ለሚፈራ ሰው መገሰጫ ይኾን ዘንድ (አወረድነው)፡፡
M.Sadiq 20:3
4
ምድርንና የላይኛዎቹን ሰማያት ከፈጠረ አምላክ ተወረደ፡፡
M.Sadiq 20:4
5
(እርሱ) አልረሕማን ነው በዐርሹ ላይ (ስልጣኑ) ተደላደለ፡፡
M.Sadiq 20:5
6
በሰማያት ያለው፣ በምድርም ያለው፣ በመካከላቸውም ያለው፣ ከዐፈር በታችም ያለው ሁሉ የርሱ ብቻ ነው፡፡
M.Sadiq 20:6
7
በንግግር ብትጮህ (አላህ ከጩኸቱ የተብቃቃ ነው)፡፡ እርሱ ምስጢርን በጣም የተደበቀንም ያውቃልና፡፡
M.Sadiq 20:7
8
አላህ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ ለእርሱ መልካሞች የኾኑ ስሞች አልሉት፡፡
M.Sadiq 20:8
9
የሙሳም ወሬ በእርግጥ መጥቶሃል፡፡
M.Sadiq 20:9
10
እሳትን ባየና ለቤተሰቦቹ፡- (እዚህ) «ቆዩ፤ እኔ እሳትን አየሁ፡፡ ከእርሷ ችቦን ላመጣላችሁ፤ ወይም እሳቲቱ ዘንድ መሪን ላገኝ እከጅላለሁ» ባለጊዜ (አስታውስ)፡፡
M.Sadiq 20:10
11
በመጣትም ጊዜ «ሙሳ ሆይ» በማለት ተጠራ፡፡
M.Sadiq 20:11
12
«እኔ ጌታህ እኔ ነኝ መጫሚያዎችህንም አውልቅ፡፡ አንተ በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ ነህና፡፡
M.Sadiq 20:12
13
«እኔም መረጥኩህ፤ የሚወረድልህንም ነገር አዳምጥ፡፡
M.Sadiq 20:13
14
«እኔ አላህ እኔ ነኝ ያለ እኔ አምላክ የለምና ተገዛኝ፡፡ ሶላትንም (በእርሷ) እኔን ለማውሳት ስገድ፡፡
M.Sadiq 20:14
15
«ሰዓቲቱ በእርግጥ መጪናት፡፡ ልደብቃት እቃረባለሁ፡፡ ነፍስ ሁሉ በምትሠራው ነገር ትመነዳ ዘንድ (መጭ ናት)፡፡
M.Sadiq 20:15
16
«በእርሷ የማያምነውና ዝንባሌውን የተከተለውም ሰው ከእርሷ አያግድህ ትጠፋለህና፡፤
M.Sadiq 20:16
17
«ሙሳ ሆይ! ይህችም በቀኝ እጅህ ያለችው ምንድን ናት» (ተባለ)፡፡
M.Sadiq 20:17
18
«እርሷ በትሬ ናት፡፡ በእርሷ ላይ እደገፍባታለሁ፣ በእርሷም ለፍየሎቼ ቅጠልን አረግፍባታለሁ፣ ለእኔም በእርሷ ሌሎች ጉዳዮች አሉኝ» አለ፡፡
M.Sadiq 20:18
19
(አላህም) «ሙሳ ሆይ! ጣላት» አለው፡፡
M.Sadiq 20:19
20
ጣላትም፡፡ ወዲያውም እርሷ የምትሮጥ እባብ ኾነች፡፡
M.Sadiq 20:20
21
«ያዛት፤ አትፍራም፡፡ ወደ መጀመሪያ ጠባይዋ እንመልሳታለን» አለው፡፡
M.Sadiq 20:21
22
«እጅህንም ወደ ብብትህ አግባ፡፡ ሌላ ተዓምር ስትኾን ያለነውር ነጭ ኾና ትወጣለችና፡፡
M.Sadiq 20:22
23
«ከተዓምራቶቻችን ታላቋን እናሳይህ ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡
M.Sadiq 20:23
24
«ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡»
M.Sadiq 20:24
25
(ሙሳም) አለ «ጌታዬ ሆይ! ልቤን አስፋልኝ፡፡
M.Sadiq 20:25
26
«ነገሬንም ለእኔ አግራልኝ፡፡
M.Sadiq 20:26
27
«ከምላሴም መኮላተፍን ፍታልኝ፡፡
M.Sadiq 20:27
28
«ንግግሬን ያውቃሉና፡፡
M.Sadiq 20:28
29
«ከቤተሰቦቼም ለእኔ ረዳትን አድርግልኝ፡፡
M.Sadiq 20:29
30
«ሃሩንን ወንድሜን፡፡
M.Sadiq 20:30